በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ስራ አጠናክሮ ለማስቀጠል የተቀናጀ ርብርብ እንደሚያስፈልግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ የኮሪደር ልማት ስራን በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ከተሞች ተግባራዊ ማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮችና የዝግጅት ሂደት ላይ ያተኮረ ውይይት በአርባምንጭ ከተማ እያካሄዱ ነው። አቶ ጥላሁን ከበደ በዚህ ወቅት፣ ከተሞች ለነዋሪዎቻቸው ምቹና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የኮሪደር ልማት ስራን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል። የተሻለ ከተማ ለቀጣይ ትውልድ ለማስረከብ እየተደረገ ላለው ሂደት የኮሪደር ልማት ስራ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው፤ ለዚህም የከተማ ነዋሪዎችና የስራ አመራሩ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በውይይቱ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሰተፉ መሆኑን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በክልሉ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት አጠናክሮ ለማስቀጠል የተቀናጀ ርብርብ ያስፈልጋል – አቶ ጥላሁን ከበደ

More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።