በ6ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል አቻ ተለያይተዋል፡፡ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በዮስኮ ጋቫርዲዮል ጎል ቀዳሚ መሆን ቢችልም ከእረፍት መልስ አንቶኒ ጎርደን ፍፁም ቅጣት ምቱን ወደ ጎል ቀይሮ ባለሜዳዎቹን አቻ አድርጓል፡፡ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ፕሪሚየርሊጉን በ14 ነጥብ በጊዜያዊነት መምራት ሲችል ኒውካስል ነጥቡን ወደ 11 ከፍ በማድረግ 5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡የሊጉ 6ኛ ሳምንት መርሃግብሮች መካሄዳቸውን ሲቀጥሉ አርሰናል ከሌስተር ሲቲ፣ብረንትፎርድ ከዌስትሃም፣ቼልሲ ከብራይተን፣ኤቨርተን ከክሪስታል ፓላስ፣ኖቲንገሃም ፎረስት ከፉልሃም እንዲሁም ወልቭስ ከሊቨርፑል ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ ነጥብ ተጋሩ

More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አንድሬ ኦናና ከቅድመ ውድድር ዘመን ጨዋታዎች ውጪ ሆነ