በ6ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል አቻ ተለያይተዋል፡፡ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በዮስኮ ጋቫርዲዮል ጎል ቀዳሚ መሆን ቢችልም ከእረፍት መልስ አንቶኒ ጎርደን ፍፁም ቅጣት ምቱን ወደ ጎል ቀይሮ ባለሜዳዎቹን አቻ አድርጓል፡፡ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ፕሪሚየርሊጉን በ14 ነጥብ በጊዜያዊነት መምራት ሲችል ኒውካስል ነጥቡን ወደ 11 ከፍ በማድረግ 5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡የሊጉ 6ኛ ሳምንት መርሃግብሮች መካሄዳቸውን ሲቀጥሉ አርሰናል ከሌስተር ሲቲ፣ብረንትፎርድ ከዌስትሃም፣ቼልሲ ከብራይተን፣ኤቨርተን ከክሪስታል ፓላስ፣ኖቲንገሃም ፎረስት ከፉልሃም እንዲሁም ወልቭስ ከሊቨርፑል ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ ነጥብ ተጋሩ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።