የቱሪዝም መረጃ የሚያዝበት”የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት” ዝግጅት ተጠናቅቆ በዛሬው ዕለት ይፋ ተደርጓል፡፡የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ ስለሺ ግርማ በሰጡት መግለጫ ÷ኢጋድ እና አባል ሀገራቱ ዘላቂ የቱሪዝም ልማትን በቀጣናው እውን ለማድረግ ዘላቂ የቱሪዝም ማስተር ፕላን ሲያዘጋጁ መቆየታቸውን ገልጸዋል ።በቀጣዮቹ 10 ዓመታት የሚተገበረው ማስተር ፕላኑ የቀጣናው ሀገራት የተቀናጁና ተወዳዳሪ የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዲሆኑ ያስችላል ተብሏል፡፡ማስተር ፕላኑ የፊታችን መስከረም 9 ቀን 2017 ዓ.ም ይፋ የሚደረግ ሲሆን÷ከዚህ ጎን ለጎንም ከመስከረም 7 እስከ 9 ቀን የኢጋድ ቱሪዝም ዓውደ ርዕይ እንደሚካሄድ ጠቅሰዋል።ኢትዮጵያ ይህንን ዓውደ ርዕይ ማዘጋጀቷ ሀገራት በአዲስ አበባ የቱሪዝም ሃብታቸውን እንዲያስተዋውቁና የንግድ ትስስር ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።በዕለቱ የቱሪዝም መረጃ የሚያዝበት “የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት” ዝግጅት ተጠናቅቆ ይፋ የተደረገ ሲሆን÷ አካውንቱን አዘጋጅቶ ለማጠናቀቅ አንድ ዓመት ከ6 ወር ያህል ጊዜ መውሰዱ ተመላክቷል፡፡የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት በዘርፉ ያሉ አጠቃላይ መረጃዎችን በአግባቡ ለመሰነድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተገልጿል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።