የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሀገር ዕድገት እና ብልፅግና ወሳኝ ድርሻ አለው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ ገለጹ፡፡
አቶ አሕመድ ሺዴ በቅርቡ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ከኢፌዴሪ አየር ኃይል የተለያዩ ክፍሎች ከተውጣጡ የሰራዊቱ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ በሰጡት ማብራሪያ÷ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቁም ባለፈ የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል።
ይህም የኢትዮጵያን ዕድገት እና ብልፅግናን ወደ ተሻለ ከፍታ እንደሚያሸጋግር ተናግረዋል።
የኢፌዴሪ አየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው÷ በተቋሙ ያሉ የሰራዊቱ አመራሮች የመንግስትን የኢኮኖሚ ፖሊሲ በበቂ ሁኔታ መረዳታቸው ቀጣይ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲመሩ እንደሚያስችል መጥቀሳቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።