የባህላዊ ትውፊትና የጥበብ ማህደር በሆነችው አክሱም የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን፣ ባህላዊና ሕዝባዊ በዓላት ትውፊታቸውን ሳይቀይሩ በማልማት ወደ ሕዝባዊ ጥቅም እንቀይርቸዋለን ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። በአክሱም ከተማና አካባቢው የዓይኒዋሪ የልጃገረዶች በዓል የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና በኢትዮጵያ የጣልያን አምባሳደር በተገኙበት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ከአክሱም ከተማና ከማዕከላዊ ዞን ሁሉም ወረዳዎች የተውጣጡ የዓይኒዋሪ ልጃገረዶች የተለያዩ አልባሳት ለብሰውና በጌጣጌጥ ደምቀው በዓሉን እያከበሩ ናቸው። ዛሬ በተጀመረው በዚሁ በዓል ላይ አቶ ጌታቸው ረዳ እንደገለጹት፤ የአክሱም ልጃገረዶች ዓይኒዋሪን በዓል ከዘመን ዘመን በቅብብሎሽ ሲያከብሩትና ሲያደምቁት ቆይተዋል። አክሱም የባህላዊ ትውፊትና የጥበብ ማህደር መሆኗን ጠቁመው፤ ለቀጣይም የቱሪስት ማዕከል ለማድረግ ልንሰራ ይገባናል ብለዋል።
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።