በኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት የምሥራቅ ዕዝ ባለፉት 47 ዓመታት ያስመዘገባቸውን አንጸባራቂ ድሎችና በተሳተፈባቸው ታላላቅ የልማት ሥራዎች ያገኛቸውን ስኬቶች ከሕዝብ ጋር በጋራ እያከበረ መሆኑን አስታወቀ።ዕዙ የተመሰረተበትን 47ኛ ዓመት በዓል ማክበር ጀምሯል፡፡የምስረታ በዓሉን አስመልክተው የዕዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል መሐመድ ተሰማ በሰጡት መግለጫ÷ ዕዙ ሀገርን አደጋ ላይ የሚጥሉ ጥቃቶችን በመመከትና ድል በማስመዝገብ ያለፉትን 47 ዓመታት ታሪክ ሲያስመዘግብ መቆየቱን አስገንዝበዋል፡፡ሕዝባዊ ወገንተኝነቱን በተግባር በማረጋገጥ አስደናቂ ታሪክ ሲያስመዘግብ መቆየቱንም አንስተዋል፡፡ዕዙ ያስመዘገባቸው ድሎችን ከሕዝቡ ጋር በጋራ ለመዘከር 47ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እያከበረ ነው ማለታቸውን የመከላከያ ሠራዊት ማኅበራዊ ትስር ገጽ መረጃ አመላክቷል፡፡በአከባበሩ ላይም ዕዙ ያስመዘገባቸውን ድሎች በመያዝ ቀጣይ ግዳጅን በድል መወጣት የሚያስችል ተጨማሪ አቅም ለመፍጠር የሕዝቡንና የሰራዊቱን አንድነት የበለጠ አጠናክሮ ለማስቀጠል ይሠራል ብለዋል፡፡ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዻጉሜን 2 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በሚከበረው በዓል ላይ÷ የትግል ሂደቱን በሚገባ የሚገልጽ ዶክመንተሪ፣ የተለያዩ ዝግጅቶች፣ ሰማዕታትን የሚዘክርና አሁን ያሉትን ጀግኖች በግልጽ አጉልቶ የሚያወጣ የፎቶግራፍ ዐውደ ርዕይ ይቀርባል ብለዋል፡፡ዕዙ በጦርነት ዐውድ ላይ የተጠቀማቸው የቡድን የጦር መሳሪያዎች እንደሚጎበኙ እና በጅግጅጋና ሐረር ከተሞች ያከናወናቸው የልማት ፕሮጀክቶችም እንደሚመረቁ አመላክተዋል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።