ሳይበር አቬንጀርን የሚል ስያሜ ያላቸው ኢራናዊያን የእስራኤል እና አሜሪካ ተቋማትን ኢላማ አድርገዋል
የቡድኑ አባላት የኢራን አብዮት ጠባቂ ጦር ስር የተዋቀሩ ናቸው ተብሏል
አሜሪካ የኢራን መረጃ መንታፊዎችን ለጠቆመኝ 10 ሚሊዮን ዶላር እሰጣለሁ አለች፡፡
የአሜሪካ ፍትህ ቢሮ እንዳስታወቀው በተደጋጋሚ በተቋማት ላይ የበይነ መረብ ጥቃት በሚያደርሱ የኢራን ሳይበር ቡድን ላይ የእስር ማዘዣ አውጥቷል፡፡
ቢሮው አክሎም እነዚህ መሰረታቸውን ኢራን ያደረጉ የሳይበር ጥቃት ቡድን ያሉበትን ለጠቆመ 10 ሚሊዮን ዶላር በወሮታ መልኩ እከፍላለሁ ብሏል፡፡
እንደ ሮይተርስ ዘገባ ይህ የመረጃ መንታፊዎች ቡድን በኢራን አብዮት ጥበቃ ጦር ስር የተደራጀ ሲሆን የአሜሪካ እና እስራኤል ተቋማትን በማጥቃት ይታወቃል፡፡
እስካሁን ባደረሳቸው የበይነ መረብ ጥቃቶችም ተቋማት መደበኛ ስራቸውን እንዳይሰሩ ማስተጓጎልን ጨምሮ ጥብቅ መረጃዎችን ሲመነትፍ እንደነበርም ተገልጿል፡፡
ስድስት አባላት ያሉት ይህ አደገኛ የመረጃ መንታፊዎች ቡድን በተለይም የእስራኤል እና አሜሪካ የሎጅስትክ ተቋማትን ኢላማ ሲያደርግ እንደነበር በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡
AL AIN
More Stories
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡
ኢራን በእስራኤል ጥቃት የተገደሉባት የኒውክሌር ሳይንቲስቶች ቁጥር 10 ደረሰ