የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በድሬዳዋ አስተዳደር ከነሐሴ 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ አጀንዳ ማሰባሰብ እንደሚጀምር አስታወቀ።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽነር አምባሳደር መሐመድ ድሪር በሰጡት መግለጫ÷ ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም በከተማው ከሚገኙ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሚሳተፉ ተወካዮች አስመርጦ ማዘጋጀቱን አስታውሰዋል፡፡
በመሆኑም ኮሚሽኑ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር በሚያከናውነው የአጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ የማህበረሰብ ወኪሎች፣ የመንግስት አካላት፣ ፓርቲዎች የተለያዩ ተቋማት እና ማህበራት ተወካዮች እንዲሁም ታዋቂ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ይመክራሉ፡፡
በዚህ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ 1 ሺህ የሚደርሱ ዜጎች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል።
አጀንዳ ማሰባሰቡ ከሰኞ ጀምሮ ለስድስት ቀናት የሚቀጥል ሲሆን÷ የአስተዳደሩ ነዋሪዎች የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ በንቃት እንዲሳተፋ መልዕክት ተላልፏል።
ምክክሩ መሰረታዊ የሆኑና አንኳር ጉዳዮችን ለመለየት እንደሚያግዝም ተመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።