ጎንደር ከተማ እስራኤል ከሚገኙ እህት ከተሞች ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ምክክር ተካሂዷል፡፡የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ባዩህ አቡሃይ ከእስራኤል ም/አምባሳደር ቶመር ባርላቪ ጋር በቱሪዝምና የእህትማማች ከተሞችን ማጠናከር በሚቻልብት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል፡፡ከዚህ ባለፈም የልማት እንቅስቃሴዎችን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን የጎንደር ከተማ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡ምክክሩ ጎንደር ከተማ እስራኤል ካሉ እህት ከተሞች ጋር ያላትን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።