ሶስተኛ ቀኑን የያዘው የአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ስልጠና በዛሬው ዕለት በመደመር ትውልድ እና የውጭ ግንኙነት ፓሊሲ አንኳር መርሆዎች ላይ አተኩሮ ተካሂዷል። በመደመር መንገድ በውጭ ግንኙነት ስራዎች ባለፉት አመታት በተገኙ ስኬቶች እና የተግባር ለውጦች ዙሪያ ለአምባሳደሮቹ ገለፃ ተደርጓል። መደመር አገር በቀል እሳቤ መሆኑን በመገንዘብ በዲፕሎማሲው መስክ ሃገራዊ ክብርን እና ጥቅምን ለማስጠበቅ በትጋት ሊሰራ እንደሚገባም በመድረኩ ተነስቷል። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፓሊሲ ዓለምአቀፍ አሰላለፍን በመገንዘብ ከፉክክር ይልቅ ትብብርን በማስቀደም መሰረታዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ የሚያስችል መሆኑ ተብራርቷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ መድረኩን በአወያይነት መምራታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …