የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 54 ሺህ 795 ሜትሪክ ቶን የታጠበና ያልታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ፡፡
አጠቃላይ አቅርቦቱም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንፃርም የ28 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ነው የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያስታወቁት፡፡
እየተሻሻለ የመጣው የቡና ማሳ እንክብካቤ፣ በክልሉ የቡና ቅምሻና ሰርቲፊኬሽን ማዕከል ሥራ መጀመር፣ የኮንትሮባንድ ንግድ ቁጥጥር መጠናከር እንዲሁም በግብይት ሂደት ያጋጥሙ የነበሩ ማነቆዎችን መፍታት መቻሉ ለምርት ዕድገቱ አስተዋፅኦ ማበርከቱንም አብራርተዋል፡፡
በ2017 የበጀት ዓመትም ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለገበያ ለማቅረብ በተሻለ አቅም እና ተነሳሽነት መሥራት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል፡፡
FBC
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ