አዲሱ የብሪታኒያ ጠ/ሚኒስትር “ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ የመላክ እቅድ በይፋ ተሰርዟል” አሉ
ጠቅላይ ሚንስትር ኬር ስታርመር ስራ ከጀመሩ በኋላ በሰጡት የመጀመሪያ መግለጫቸው በቀድሞው የወግ አጥባቂ መንግስት ቀርቦ የነበረው አወዛጋቢው የሩዋንዳ የስደት ፖሊሲ መሰረዙን አስታውቀዋል።
ስታርመር ውጤታማ ያልሆኑ እና ኢሰብአዊ የሆኑ የኢሚግሬሽን እርምጃዎችን ለማስቆም ቁርጠኛ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል ነው የተባለው።
ጠቅላይ ሚንስትር ኬር ስታርመር በዳውኒንግ ስትሪት ጽህፈት ቤታቸው ባደረጉት ንግግር የሩዋንዳው የስደተኞች እቅድ ገና ከጅምሩ ሞቶ የተቀበረ ነው ብለዋል።
Al-Ain
More Stories
አራተኛው ዙር የኢራን እና የአሜሪካ ድርድር ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ
ሩሲያ በዩክሬን የኢነርጂ መሰረተ ልማት ተቋማት ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት ለማቆም ተስማማች