የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ሞተራይዝድ ሻለቃ አሁን ላይ ያለበትን ዝግጁነት ጎብኝተዋል። ፊልድ ማርሻሉ በጉብኝታቸው ሞተራይዝድ ሻለቃው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስታንዳርድ መሰረት ዝግጁነት ላይ እንደሚገኝ መመልከታቸውን ተናግረዋል። ሞተራይዝድ ሻለቃው በተሟላ የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የተናገሩት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፤ ሻለቃው ለማንኛውም ተልዕኮ ዝግጁ መሆኑን ለማረጋገጥ መቻላቸውንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ በተለይም ለምስራቅ አፍሪካ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አበርክቶ እንደነበራትም ፊልድ ማርሻሉ አስታውሰዋል።
ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም መረጋገጥ በሙሉ ዝግጁነት ላይ እንደምትገኝ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ገለፁ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።