በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ጅቡቲ የገባ ሲሆን ከጅቡቲ አቻቸው ማህሙድ አሊ የሱፍ ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም፤ ሁለቱ ወገኖች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማጠናከር እና ቁልፍ ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ የወደብ አገልግሎቶችን በተመለከተ ያላቸውን ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር መደረጉን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል።
EBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …