የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከሃይማኖት አባቶች እና በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ዞኖች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች እና ተፅኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ በመወያየት ላይ ይገኛሉ፡፡ መድረኩ “የአባቶች ሚና በልዩነት ለተዋበ ጠንካራ የህዝቦች አንድነት” በሚል መሪ ቃል ነዉ እየተካሄደ የሚገኘው። ክልሉ የሰላም የመቻቻል እና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየተደረገ ላለው ጥረት የሀገር ሽማግሌዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል። በውይይቱ ከርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፤ የዞን አመራሮች፤ የሃይማኖት አባቶች፤ የሀገር ሽማግለዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መገኘታቸውን ከክልሉ ኮሙዪኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ