የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከሃይማኖት አባቶች እና በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ዞኖች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች እና ተፅኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ በመወያየት ላይ ይገኛሉ፡፡ መድረኩ “የአባቶች ሚና በልዩነት ለተዋበ ጠንካራ የህዝቦች አንድነት” በሚል መሪ ቃል ነዉ እየተካሄደ የሚገኘው። ክልሉ የሰላም የመቻቻል እና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየተደረገ ላለው ጥረት የሀገር ሽማግሌዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል። በውይይቱ ከርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፤ የዞን አመራሮች፤ የሃይማኖት አባቶች፤ የሀገር ሽማግለዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መገኘታቸውን ከክልሉ ኮሙዪኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።