የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከሃይማኖት አባቶች እና በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ዞኖች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች እና ተፅኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ በመወያየት ላይ ይገኛሉ፡፡ መድረኩ “የአባቶች ሚና በልዩነት ለተዋበ ጠንካራ የህዝቦች አንድነት” በሚል መሪ ቃል ነዉ እየተካሄደ የሚገኘው። ክልሉ የሰላም የመቻቻል እና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየተደረገ ላለው ጥረት የሀገር ሽማግሌዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል። በውይይቱ ከርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፤ የዞን አመራሮች፤ የሃይማኖት አባቶች፤ የሀገር ሽማግለዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መገኘታቸውን ከክልሉ ኮሙዪኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።