የማሻ ወረዳ ግብርናና አከባቢ ጥበቃ ጽህፈት ቤት ምክትል የተፈጥሮ ሀብትና አከባቢ ጥበቃ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መብራቴ ጨጊቶ በወረዳው ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የችግኝ ተከላ ስራ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብር የቡና ፣ የመኖ እጽዋት ፣የአቦካዶ እና የተለያዩ የደን ዝሪያዎች እንደሚተከሉ ገልጸው እነዚህ ችግኞች ኢኮኖሚያዊና ኢኮሎጅያዊ ፋይዳ ያላቸው መሆኑን ጠቁመዋል::በወረዳው የቡና ችግኝ ጨምሮ 5 ነጥብ 1ሚልዮን ለመትከል እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው 1 ነጥብ 9 ሚልዮን የቡና ችግኝና 3 ነጥብ 2 ሚልዮን የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያላቸው ችግኞች በተራቆቱ ቦታዎች የሚተከሉ መሆኑን ተናግረዋል::በዚህም 803 ሄክታር በላይ መሬት ለመሸፈን ዕቅድ መያዙን በማንሳት የተለያዩ ፕሮጀክቶች በወረዳው በችግኝ ማዘጋጀት ላይ የተሰማሩ መሆናቸውንም አብራርተዋል።ከአሁን በፊት በተለያዩ ጊዜያት የተተከሉ ችግኞች በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የገለፁት የጽ/ቤቱ ምክክትል ኃላፊ የጽድቀት መጠኑ 85 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል:: የአለም የአየር ንብረት ለውጥ በሰው ልጆች ላይ የተለያዩ አሉታዊ ጫናዎችን እያሳደረ በመሆኑ የተፈጥሮ ሚዛን ለመጠበቅ ሁሉም የየራሱን ተሳትፎና አበርክቶ ልያደርግ እንደሚገባም ተናግረዋል ።
ዘጋቢ ልጃለም ማሞ
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።