ከ120 ሚሊየን በላይ ሕዝብ ላላት ኢትዮጵያ መድኃኒቶችን በራስ ዐቅም ማምረት ለነገ የሚተው ጉዳይ አይደለም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሀገር ውስጥ የሕክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ዐውደ-ርዕይን መርቀው ከፍተዋል፡፡ይህን ተከትሎም በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ የሀገር ውስጥ የሕክምና ግብዓቶችንና እና መድኃኒቶችን ለማምረት የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ከማድረግ ጀምሮ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።እንዲሁም መድኃኒት እና የሕክምና ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን አስቻይ ሁኔታዎች መዘጋጀታቸውን በዐውደ-ርዕዩ ላይ ባደረጉት ንግግር አስታውቀዋል፡፡”ጤናችን በምርታችን” በሚል መሪ ሐሳብ የተከፈተውን ዐውደ-ርዕይ የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ መድኃኒት አምራቾች ማኅበር በጋራ አዘጋጅተውታል፡፡ለሥድስት ቀናት ለሕዝብ ክፍት ሆኖ በሚቆየው ዐውደ-ርዕይ ላይ÷ ከ110 በላይ የዘርፉ አምራቾች እንደሚሳተፉበት ተገልጿል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።