ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን በማልማት ተረጂነትን ለማስቀረት የጀመረችውን ግብ ለማሳካት አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሠራ እንደሚገባ ተመላከተ፡፡የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ አመራሮች “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት” በሚል መሪ ሐሳብ እየተወያዩ ነው፡፡በውይይቱም ከተረጂነት አስተሳሰብ መላቀቅ እና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሚገባ በአጽንኦት ተገልጿል፡፡የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት÷ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር እንደ ሀገር ያሉ እምቅ ሃብቶችን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡ተረጂነትን ማስቀረት እንደሚቻልም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም የልማት ሥራዎች የተመዘገቡ ውጤቶች ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡የሀገር ሉዓላዊነት ምልዑ የሚሆነው የተረጂነት አስተሳሰብን በማስወገድ እና ምርታማነትን በእጅጉ በማሳደግ ራስን የመቻል ግብ ሲረጋገጥ መሆኑን አመላክተው÷ ከዚህ አኳያ አመራሩ ትልቅ ኃላፊነት አለበት ብለዋል።የዛሬው ውይይት ዓላማም አመራሩ ከተረጂነት ለመላቀቅና ምርታማነትን ለማሳደግ የመሪነት ሚናውን በአግባቡ እንዲወጣ መግባባት ለመፍጠር ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።