ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን በማልማት ተረጂነትን ለማስቀረት የጀመረችውን ግብ ለማሳካት አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሠራ እንደሚገባ ተመላከተ፡፡የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ አመራሮች “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት” በሚል መሪ ሐሳብ እየተወያዩ ነው፡፡በውይይቱም ከተረጂነት አስተሳሰብ መላቀቅ እና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሚገባ በአጽንኦት ተገልጿል፡፡የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት÷ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር እንደ ሀገር ያሉ እምቅ ሃብቶችን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡ተረጂነትን ማስቀረት እንደሚቻልም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም የልማት ሥራዎች የተመዘገቡ ውጤቶች ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡የሀገር ሉዓላዊነት ምልዑ የሚሆነው የተረጂነት አስተሳሰብን በማስወገድ እና ምርታማነትን በእጅጉ በማሳደግ ራስን የመቻል ግብ ሲረጋገጥ መሆኑን አመላክተው÷ ከዚህ አኳያ አመራሩ ትልቅ ኃላፊነት አለበት ብለዋል።የዛሬው ውይይት ዓላማም አመራሩ ከተረጂነት ለመላቀቅና ምርታማነትን ለማሳደግ የመሪነት ሚናውን በአግባቡ እንዲወጣ መግባባት ለመፍጠር ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
FBC
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ