የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኳታር ዶሃ የሚገኘው የዶክ ሕክምና ማዕከል መስራች በሆኑት ዶ/ር ኢማኑኤል ቶሎሳ ከተመራ የልዑካን ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል። የሕክምና ማዕከሉ በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ በኢንቨስትመንት መሰማራት በሚችልበት ሁኔታ ላይ የሀሳብ ልውውጥ ተደርጓል።ማዕከሉ በዓይነቱ ልዩ የሆነ እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የአጥንት ህክምና ማዕከል በኢትዮጵያ ለማቋቋም ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል። ዶክ በኳታር ከኦርቶፔዲክ፣ ሩማቶሎጂ፣ ኒውሮሎጂ፣ ኒውሮፊዚዮሎጂ፣ ፊዚዮቴራፒ፣ ካይሮፕራክቲክ እና የጥርስ ሕክምና ጋር የተያያዙ የምርምራ እና የሕክምና አገልግሎቶችን የሚሰጥ ትልቁ የጤና ማዕከል መሆኑን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።