የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኳታር ዶሃ የሚገኘው የዶክ ሕክምና ማዕከል መስራች በሆኑት ዶ/ር ኢማኑኤል ቶሎሳ ከተመራ የልዑካን ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል። የሕክምና ማዕከሉ በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ በኢንቨስትመንት መሰማራት በሚችልበት ሁኔታ ላይ የሀሳብ ልውውጥ ተደርጓል።ማዕከሉ በዓይነቱ ልዩ የሆነ እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የአጥንት ህክምና ማዕከል በኢትዮጵያ ለማቋቋም ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል። ዶክ በኳታር ከኦርቶፔዲክ፣ ሩማቶሎጂ፣ ኒውሮሎጂ፣ ኒውሮፊዚዮሎጂ፣ ፊዚዮቴራፒ፣ ካይሮፕራክቲክ እና የጥርስ ሕክምና ጋር የተያያዙ የምርምራ እና የሕክምና አገልግሎቶችን የሚሰጥ ትልቁ የጤና ማዕከል መሆኑን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።