ግዙፉ የአውሮፕላን አማራች ኩባንያ ቦይንግ፤ የአፍሪካ ዋና መቀመጫውን በኢትዮጵያ ሊከፍት መሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡ የኩባንያው ውሳኔ ተቋሙ ዋና መቀመጫውን በኬኒያ አሊያም በደቡብ አፍሪካ ሊያደርግ እንደሚችል ሲሰጡ የነበሩ ግምቶችን ያስቀረ እና ኢትዮጵያ ቀዳሚ ምርጫው መሆኗን ያረጋገጠ ነው፡፡ እ.አ.አ በ2023 ኢትዮጵያ እና ቦይንግ ኩባንያ የተወሰኑ የአውሮፕላን ክፍሎችን ኢትዮጵያ ውስጥ ለማምረት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ይታወሳል፡፡ የአፍሪካ አየር መንገዶች በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ1 ሺህ በላይ አዳዲስ አውሮፕላኖችን እንደሚፈልጉ የኩባንያው ጥናት ያመላክታል፡፡ ከእነዚህ ወስጥ 80 በመቶ የሚሆኑት አዳዲስ አውሮፕላኖች የአየር መንገዶቹን መዳረሻ ለማስፋት እንደሚያገለግሉ ዲደብሊው አፍሪካ ዘግቧል፡፡
EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ