የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የስራ እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል፡፡
ጉብኝቱን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት ÷ በግብርና ዘርፍ ያገኘናቸው ስኬቶች በኢንዱስትሪው ዘርፍም በመደገም ላይ ናቸው ብለዋል።
በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የተካሄደውን የመዋቅር እና የአመራር ለውጥ ተከትሎ ተቋሙ ሪቨርስ ኢንጂነሪንግ ዘዴን በመጠቀም የተለያዩ መሳሪያዎችን፣ ሮኬቶችን እና ታንኮችን ለማምረት አስደናቂ ስራ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
እያደጉ ያሉ አቅሞች ብልፅግናን ከማረጋገጥ በተጨማሪ ለአህጉራችን ተስፋ እየሆኑ ነውም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡
አክለውም ፥ በስኬቶቻችን ላይ በመመስረት እና በሰፊ የሰው ኃይላችን በመደገፍ በሁሉም ዘርፎች እና መስኮች እድገታችንን ማፋጠን ይኖርብናል ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።