አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ያነሷቸው ወቀሳዎች በተሳሳቱ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ነው ብሏል የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
አምባሳደሩ በኢትዮጵያ የንጹሃን ግድያ፣ ያለህጋዊ አግባብ የሚፈጸም እስርና ስወራ በአፋጣኝ እንዲቆም ማሳሰባቸው ይታወሳል
አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ ትናንት በአሜሪካ ግቢ ባደረጉት “የሰብአዊ መብትና ምክክር የፖሊስ ንግግር” ያነሷቸው ወቀሳዎች በሀሰተኛ መረጃ የተመሰረተ ነው ብሏል የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዛሬው እለት ባወጣው መግለጫ።
አምባሳደር ኢርቪን “ኢትዮጵያ ሳትጠይቃቸው የውስጥ ችግሯን እንዴት ትፍታው የሚል ምክርን ሲለግሱ ታይተዋል” የሚለው መግለጫው፥ በምርጫ ስልጣን ላይ ያለውን የኢትዮጵያ መንግስት ንጹሃንን ከሚያግቱና ከሚያሸብሩ አካላት ጋር መጥቀሳቸውም ተገቢ አለመሆኑን አብራርቷል።
Al-Ain
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።