“ከታሪካዊ መሰረትዎ ጋር ይገናኙ” በሚል መሪ ሃሳብ ወደ ሀገራቸው የመጡ የ2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን የፓናል ውይይት በዓድዋ ድል መታሰቢያ ተካሂዷል። መርሀግብሩ 2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውን ከታሪካዊ መሰረታቸው ጋር እንዲገናኙ እና ስለሀገራቸው እንዲያውቁ ለማድረግ የተሰናዳ ነው።በመርሀግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ እንዲሁም ከተለያዩ አገራት የመጡ 2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል።አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያቀረቡትን ጥሪ ተከትሎ “ከባህልዎ ጋር ይተዋወቁ” በሚል በተካሄደው የመጀመሪያው ዙር መርሀግብር በርካታ 2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ቤት መምጣታቸውን አስታውሰዋል።2ኛ ትውልድ ኢትዮጵያውያኑ ከታሪካዊ መሰረታቸው ጋር እንዲገናኙ በተሰናዳው ሁለተኛው ዙር መርሀግብርም በርካታቶች ወደ ሀገራቸው መምጣታቸውን ተናግረዋል። የቱሪዝም ሚኒስትሯ በንግግራቸው፥ ኢትዮጵያ የሚያኮሩ በርካታ ባህሎች እንዳሏት አንስተዋል። የአዲስ አበባ ከተባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው፥ በኢትዮጵያ ትልልቅ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ፤ ሀገሪቱም በለውጥ ጎዳና ላይ እየተራመደች መሆኑን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የሚያኮራ ትልቅ ታሪክ እንዳላት የጠቀሱት ከንቲባዋ፤ ያለፉ ስህተቶች ቢኖሩ እንኳ ከመራራቅ ይልቅ ተቀራርቦ በመነጋገር በጋራ ማረም እንደሚገባ ጠቁመዋል።ለዳያስፖራ አባላቱ የኢትዮጵያን ታሪክ እና ለሀገራቸው ሊያበረክቱት የሚችሉትን አስተዋጽኦ የተመለከተ የመነሻ ገለፃ ቀርቦላቸው ተወያይተውበታል።
EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ