በአዘርባጃን በይፋዊ የሥራ ጉብኝት ላይ የሚገኙት የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከአገሪቱ የኢኮኖሚ ሚኒስትር ሚካይል ጃባሮቭ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።በውይይቱም የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ለመስራት ከስምምነት ላይ ተደርሷል።በኢትዮጵያ ያለውን አስተማማኝ የመልማት ጸጋ እና ዕድል ለመጠቀም፣ በተለይም ገቢን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት አዘርባጃን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ሚካይል ጃባሮቭ ገልጸዋል። በኢንቬስትመንትና በስትራቴጂያዊ ስራዎች ያላትን ልምድ ለማካፈልም አገሪቱ ፍላጎት እንዳላት ሚኒስትሩ ተናግረዋል።በተጨማሪም አገሪቱ በጋራ መልማት የሚያስችሉ ዕድሎችን ሁሉ ለመጠቀም ያላትን ቁርጠኝነት ማረጋገጣቸውን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።