
ኳታር ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ እንደሚፈልጉ ተገለጸ፡፡በኳታር፣ የመን እና ኢራን የኢፌዲሪ አምባሳደር ፈይሰል አልይ ከኳታር የኢንቨስትመንት ባለስልጣን የአፍሪካ ዳይሬክተር ሱልታንአል ሳዓዲ እና ልዑካቸው ጋር ተወያይተዋል፡፡አምባሳደር ፈይሰል÷ በኢትዮጵያ በሆቴል ቱሪዝም፣ በታዳሽ ኃይልና በአምራች ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት ዘርፍ የውጭ ኩባንያዎች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎች መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡የኳታር ኢንቨስትመንት ባለስልጣን የሀገሪቱ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግም ጠይቀዋል፡፡ ሱልታንአል ሳዓዲ በበኩላቸው÷ የኳታር ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው መናገራቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።