
ኳታር ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች መዋዕለ ንዋያቸውን ማፍሰስ እንደሚፈልጉ ተገለጸ፡፡በኳታር፣ የመን እና ኢራን የኢፌዲሪ አምባሳደር ፈይሰል አልይ ከኳታር የኢንቨስትመንት ባለስልጣን የአፍሪካ ዳይሬክተር ሱልታንአል ሳዓዲ እና ልዑካቸው ጋር ተወያይተዋል፡፡አምባሳደር ፈይሰል÷ በኢትዮጵያ በሆቴል ቱሪዝም፣ በታዳሽ ኃይልና በአምራች ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት ዘርፍ የውጭ ኩባንያዎች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎች መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡የኳታር ኢንቨስትመንት ባለስልጣን የሀገሪቱ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት አማራጮች መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግም ጠይቀዋል፡፡ ሱልታንአል ሳዓዲ በበኩላቸው÷ የኳታር ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው መናገራቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።