ጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ኡመድ ኡጁሉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።
ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ኡመድ ኡጁሉና ልዑካቸው በክልሉ ካፋ ዞን ውሽውሽ ሻይ ተክል ልማት አካባቢ ሲደርሱ ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ተቀብለዋቸዋል ።
ከርዕሰ መስተዳድር አቶ ኡመድ ኡጁሉ ጋር ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች አብረው ተገኝተዋል ።
ርዕሰ መስተዳድር ኡመድ ኡጁሉና ልዑካቸው በኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የውሽውሽ ሻይ ልማት የስራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በክልሉ የአስተዳደርናፖለቲካ መቀመጫ በሆነችሁ ቦንጋ ከተማ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት እና የጋምቤላ ክልል መንግስት የጋራ የሰላምና ልማት ምስረታ በነገው ዕለት ይደረጋል ሲል የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ዘግቧል።
ለተጨማሪ መረጃ ከታች ባሉት ድረ ገጾች ይከታተሉን!
Facebook=https://www.facebook.com/profile.php?id=61552831883490
telegram =https://t.me/MashaFmradio
tiktok=https://www.tiktok.com/@masha_fm103.8?_t=8h8vFNn1ToE&_r=1
YouTube=https://youtube.com/@MashaFM-op5hb?si=4gRo1QtHJYQoGZqY
Instagram=https://instagram.com/mashafm2023?igshid=MWFsc2NqcTJ2cWJhcg==
Twitter =https://twitter.com/masha_fm98
WhatsApp= https://whatsapp.com/dl/
website:www.mashafm.gov.et
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
More Stories
በቀጣይ 90 ቀናት የተቀመጡ ዕቅዶችን በውጤታማነት በመፈጸም እመርታዊ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል፦አቶ ፍቅሬ አማን
ምክር ቤቶች የህዝቡ ሁለተናዊ ተጠቃሚነት እንድረጋጥ ድርሻቸው የጎላ በመሆኑ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ማጠናከር እንደምያስፈልግ ተጠቆመ ።
ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ እያከናወነች ያለው ተግባር የሚደነቅ ነው