በሀገራዊ ምክክሩ የወጣቶችን ሁሉ አቀፍ ተሳትፎ ለማጠናከር የሚያስችል የማህበራዊ ድህረ ገጾች የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ይፋ ተደርጓል፡፡
የወጣቶች ድምጽ ለሀገራዊ ምክክር በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሄደው ንቅናቄ ወጣቶች በሀገራዊ ምክክሩ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ረገድ የመሪነት ሚና እንዲጫወቱ የሚያስችል መሆኑን ተገልጿል።
በንቅናቄው ከተለያዩ ማህበራት የተወጣጡ ወጣቶች፣ በወጣቶች ላይ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ በጎ አድራጎት ድርጅቶች፣ ወጣት የማህበረሰብ አንቂዎች፣ በሚዲያና ፈጠራ ስራ የተሰማሩ ወጣቶችን እንደሚያሳትፍ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ አመልክቷል።
የንቅናቄ መድረኩ ለሶስት ወር የሚዘልቅ ሲሆን ወጣቶችን ተደራሽ ለማድረግ የታለመ መሆኑም ተነግሯል።
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች