ከችግሮች ነፃ የሆነች ኢትዮጵያን እውን ሆና ለማየት ምክክሩ ሊያመልጠን አይገባም ሲሉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰላምና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ አለነ ገለጹ።የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን “የኢትዮጵያ ሚዲያ ለኢትዮጵያውያን ውጤታማ ሀገራዊ ምክክር” በሚል መሪ ሃሳብ ከፌዴራል፣ ከክልል፣ ከግል የሚዲያ አመራሮችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጋር እየመከረ ነው።አቶ እውነቱ፤ የምክክር ኮሚሽኑን በተመለከተ ከገለልተኝነት ጋር ተያይዞ የሚቀርብበት ወቀሳ በሕግ የተፈታ ነው ሲሉም ተናግረዋል።ኮሚሽኑ ተጠሪነቱ ለምክር ቤቱ ቢሆንም፤ ምክር ቤቱ ስራውን ከማገዝ ያለፈ ጣልቃ አይገባበትም ነው ያሉት።መገናኛ ብዙኀንም የተሳካ ምክክር እንዲደረግና ልዩነቶች በሰለጠነ መንገድ እንዲፈቱ አቅም ሊሆኑ እንደሚገባም ገልጸዋል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።