ዘላቂ እና አዎንታዊ ሰላምን ለማረጋገጥ በሚደረገው እንቅስቃሴ የተለያዩ አጋር አካላት ትብብር ወሳኝ መሆኑን የሰላም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
በሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዷለም የተመራ ልዑክ በሰሜን አሜሪካ ዩታሃ ግዛት ከሚገኘው የስተርሊንግ ፋውንዴሽን አመራሮች ጋር በሰላም ግንባታ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።
አቶ ብናልፍ አንዷለም በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በግዛቲቱ በወጣቱና አዛውንቶች እየተሰጠ ያለው የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በአካባቢው ሰላም ለማምጣትና ጠንካራ ግዛት ለመፍጠር ጉልህ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ከዚህ ተግባር እንደ ሀገር ብዙ እንደምትማር ነው ሚኒስትሩ ያስገነዘቡት፡፡
የስተርሊንግ ፋውንዴሸን በኢትዮጵያ ዘላቂና አዎንታዊ ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት እያበረከተ ያለውን አስተዋፅኦ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
የፋውንዴሽኑ ምክትል ስራ አስፈፃሚ ኒኮል እስተርሊንግ በበኩላቸው÷ መንግስት ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ ፋውንዴሽኑ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የልዑካን ቡድኑ አባላት በግዛቷ የሰብዓዊ መስጫ ማዕከላትን፣ የተለያዩ ሃይማኖቶች በመከባበርና በሰላም አብረው በአካባቢው ሰላም፣ አብሮነትና መከባበር ለማምጣት የሚያከናውኑ ተግባራትንና የተገኘውን ውጤት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በተጨማሪም በግዛቲቱ ከሚገኙ በሰላም ግንባታ ዙሪያ ከሚሰሩ የተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት አመራሮች ጋር መምከራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።