የካፈቾ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “የቤነ ሻዴዬ ባሮ”ን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ የፓናል ውይይት በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በፓናል ውይይቱ የአከባቢው ተወላጆችና ተጋባዥ እንግዶች እየታደሙ ይገኛሉ።
የካፊቾ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “የቤነ ሻዴዬ ባሮ” ከዛሬው ዕለት ጀምሮ በፓናል ውይይትና በአደባባይ እንደሚከበርም ተገልጿል።
ባህልን መጠበቅን፣ መንከባከብ እንዲሁም በአግባቡ መጠቀም ላይ ትኩረት ያደረገ ጥናታዊ ጽሁፎች በምሁራኞች እንደሚቀርብም ከወጣው መርሀግብር ለመረዳት ተችሏል።
ዘገባው የክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።