
በቅርብ የሚመረቁት የጎርጎራ ፕሮጀክት እና የዓባይ ድልድይ ለሕዝብ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ዕድል እንደሚያስገኙ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ማሥተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አደም ፋራህ ከአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች ጋር በመሆን÷ የዓባይ ወንዝ ድልድይን ጨምሮ የተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን እና የሌማት ትሩፋት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
አቶ ተመስገን በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ በባሕር ዳር ከተማ የሚሠሩ የልማት ሥራዎች ከአካባቢው ሕዝብ በተጨማሪ ለሀገርም ትልቅ ጸጋ ናቸው።
የጎርጎራ ገበታ ለሀገር ፕሮጀክት እና ውብ የሆነው የዓባይ ድልድይ በቅርቡ እንደሚመረቁ ጠቁመው÷ ለባሕር ዳር ሕዝብ ብሎም ለሀገር ትልቅ የቱሪዝም ትሩፋት እንደሚያስገኙ መናገራቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
ሕዝቡ ሰላም እና ልማት እንደሚፈልግ ገልጸው÷ ተገንብተው ከተጠናቀቁ እና ገና ከሚጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠቃሚ ለመሆን የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እና ማጽናት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ችግሮች ቢከሰቱ እና ጥያቄዎች ቢኖሩ እንኳን በሰለጠነ አግባብ እየተወያዩ የመፍታት ባህልን ማዳበር እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች