ማሻ ፣ የግንቦት 20፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የኬንያ ህገ አውጪ ምክር ቤት የኢጋድን ስምምነት ማፅደቁን የምስራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት የልማት ድርጅት (ኢጋድ) ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) አድንቀዋል።
የኢጋድ ስምምነት በሀገሪቱ ምክር ቤቱ መፅደቁ ድንበር ዘለለ ተግዳሮቶችን በመከላከል ዘላቂ ሰላምንና ብልፅግናን ለማረጋገጥ ቀጠናዊ ትብብርና ለማጠናከር ያግዛል ብለዋል።
የቀጠናው ሀገራት በጋራ ጉዳይ ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን የሚገልፁበት የኢጋድ ስምምነት ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ በጅቡቲ እና በደቡብ ሱዳን ህግ አወጪ አካላት መፅደቁ ይታወሳል።
በሀገራቱ መካከል ሰላማዊ ግንኙነትን ማረጋገጥ፣ ጤናማ ጉርብትና መፍጠር፣ በጎረቤት ሀገራት ጉዳይ ጣልቃ አለመግባት፣ በሀገራቱ መካከልም ሆነ በሀገራቱ ውስጥ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት፣ ቀጠናቂ ሰላምን መረጋጋት እንዲሁም ደህንነት ማረጋገጥ የኢጋድ ስምምነት ዋንኛ ዓላማዎች ናቸው ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።