ማሻ ፣ የግንቦት 06፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ከተረጂነት ወደ ምርታማት በመሸጋገር የተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ከሁሉም የብልጽግና አባላት እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
ከተረጂነት ወደ ምርታማት ወደ ተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነት በሚል መሪ ሀሳብ ቅጽ 1 ቁጥር 6 የልሳነ ብልጽግና ንድፈ ሀሳብ መጽሔት ላይ ከአባላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
የመወያያ ሰነዱን ያቀረቡት የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ ከተረጂነት ወደ ምርታማት በመሸጋገር የተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ከሁሉም የብልጽግና አባላት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል ።
የክልል ማዕከል አስተዳደር የብልጽግና ህብረት አመራሮችና የብልጽግና ቤተሰብ አባላት በተሳተፉበት በቀረበው የመወያያ ሰነድ ምርታማነትን በማሳደግ የተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ጥገኛ ከሆነ አስተሳሰብ ፈጥኖ መውጣት ይገባል ብለዋል።
በልሳነ ብልጽግና ንድፈ ሀሳብ መጽሔት ሀገራዊ ቁመናን፣ እሳቤያዊና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም አስቻይ ሁኔታዎች እና ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርምና አንድምታው በተሰኙ ወሳኝ ርዕሶች ላይ ገለጻ አድርገዋል ሲል የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።