ማሻ ፣ የግንቦት 06፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ከተረጂነት ወደ ምርታማት በመሸጋገር የተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ከሁሉም የብልጽግና አባላት እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
ከተረጂነት ወደ ምርታማት ወደ ተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነት በሚል መሪ ሀሳብ ቅጽ 1 ቁጥር 6 የልሳነ ብልጽግና ንድፈ ሀሳብ መጽሔት ላይ ከአባላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
የመወያያ ሰነዱን ያቀረቡት የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ ከተረጂነት ወደ ምርታማት በመሸጋገር የተሟላ ሃገራዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ከሁሉም የብልጽግና አባላት እንደሚጠበቅ አስረድተዋል ።
የክልል ማዕከል አስተዳደር የብልጽግና ህብረት አመራሮችና የብልጽግና ቤተሰብ አባላት በተሳተፉበት በቀረበው የመወያያ ሰነድ ምርታማነትን በማሳደግ የተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ጥገኛ ከሆነ አስተሳሰብ ፈጥኖ መውጣት ይገባል ብለዋል።
በልሳነ ብልጽግና ንድፈ ሀሳብ መጽሔት ሀገራዊ ቁመናን፣ እሳቤያዊና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም አስቻይ ሁኔታዎች እና ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርምና አንድምታው በተሰኙ ወሳኝ ርዕሶች ላይ ገለጻ አድርገዋል ሲል የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
More Stories
በቴፒ ከተማ ተቋቁሞ አገልግሎት እየሰጠ ያለው የመሶብ አንድ ማዕከል ከእንግልትና ከምልልስ እንደታደጋቸው ተገልጋዮች ተናገሩ
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ