በአሜሪካ ቺካጎ ተወልደው ያደጉት የ69 ዓመቱ ካርዲናል ሮበርት ፕሪቮስት፣ ፖፕ ሊዮ ተብለው የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተመረጡ።
ካርዲናል ፕሪቮስት በፔሩ ጳጳስ ሆነው ከመሾማቸው በፊት በሚሺነሪነት አገልግለዋል።
ሊቀ ጳጳሱ ከእንግሊዝኛ በተጨማሪ ጣልያንኛ እና ስፓኒሽኛ የሚናገሩ ሲሆን፣ በተለያዩ ማኅበራዊ አገልግሎታቸው እንዲሁም አዳማጭነታቸው ይጠቀሳሉ።
ከሁለት ዓመት በፊት እአአ በ2023 ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስ የቫቲካን የጳጳሳት አለቃ አድርገው በመሾም ቀጣዩን የጳጳሳት ትውልድ በመምረጥ ውስጥ ቁልፍ ሥልጣን እንዲኖራቸው አድርገዋል።
ካርዲናል ፕሮቮስት ሊቀ ጳጳስ ሊዮ 14ኛ ተብለው ለመጠራት መወሰናቸው ተገልጿል።
ለሁለት ቀናት አዲሱን ሊቀጳጳስ ለመምረጥ የተሰባሰቡት የቤተ ክርስቲያኗ ካርዲናሎች ከተሰበስቡብት ቤተ መቅደስ አናት ላይ አዲስ ሊቀ ጳጳስ መመረጡን የሚያሳየው ነጭ ጭስ የታየው ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ነበር።
የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ካርዲናሎች በምሥጢር በሚሰጡት ድምጽ ለመመረጥ በዕጩነት ከቀረቡት ካርዲናሎች መካከል ሁለት ሦስተኛውን ድምጽ ያገኙት የሃይማኖት አባት ቀጣዩ ሊቀ ጳጳስ ይሆናሉ።
አሜሪካዊው ሊቀ ጳጳስ ሊዮ 14ኛ በቫቲካን አዲሱን ሊቀ ጳጳስ ለመምረጥ ለሁለተኛ ቀን የተሰባሰቡት ካርዲናሎች በምሥጢር ድምጻቸውን መስጠታቸውን ተከትሎ ነው አዲስ ሊቀ ጳጳስ መሆናቸ ይፋ የተደረገው።
ድምጽ መስጠት ከሚችሉት 133 ካርዲናሎች መካከል የ89ኙን ይሁንታ ያገኙት ሊቀ ጳጳስ በቅዱስ ጴጥሮስ ካቴድራል በረንዳ ላይ ብቅ በማለት ለሕዝብ ታይተዋል።
በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ የተሰባሰቡ የእምነቱ ተከታዮች ሊቀ ጳጳሱን ሲመለከቱ ደስታቸውን በጩኸት እና በእንባ ገልጸዋል።
ዕድሜያቸው እስከ 80 ዓመት የሚሆን 133 ካርዲናሎች ቀጣዩ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ማን ሊሆን እንደሚገባ ከተወያዩ በኋላ ይሆናሉ ያሏቸውን በዛሬው ዕለት መርጠዋል።
ሚያዝያ 13/2017 ዓ.ም. ሕይወታቸው ያለፈው ሊቀ ጳጳስ ፍራንሲስን የተኩት አባት አሜሪካዊው ካርዲናል ሮበርት ፕሮቮስት ሆነው ተመርጠዋል።
More Stories
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በሩሲያ የድል በዓል የአቀባበል ስነ ስርዓት ላይ ተሳተፉ
የዘመኑን ዐርበኝነት እውን ለማድረግ ራስን ለመቻል በሚደረጉ የልማት ሥራዎች ዙሪያ-መለስ ትጋት ከኹሉም ዜጎች ይጠበቃል። -የኢፌዲሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰብስቤ ሻዌኖ እንኳን ለ116ኛው የኢትዮጵያ ፖሊስ ምሥረታ ቀን በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።