ማሻ ፣ የሚያዝያ 23፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በሸካ ዞን ማሻ ወረዳ የካንጋ ቀበሌ አርሶ አደሮች የኮርደር ስራ ጥቅሙን በመረዳት ትኩረት ሰጥቶ እየሰሩ ይገኛሉ።
የካንጋ ቀበሌ ሞዴል አርሶ አደር አመነ አምበሎ እንደሚሉት የቤትና ግቢውን ውቤት ለመኖሪያ ጽዱና ሚቹ አደረገው መኖር ከአባቶቻችን የወረስነው ባህላችን ቢሆንም አሁን መንግስት በሰጠው ትኩረትም ደስተኛ መሆናቸውን ይናገራሉ።
የቀለም ትምህርትን እስከ 7ተኛ ክፍል እንደተማሩ የሚናገሩት ሞዴል አርሶ አደሩ ከ6 በላይ ልጆችን በማስተማር ለተለያዩ መንግስት ስራ በማድረስ ባላቸው ዕውቀትና ትጋት ጽዱና ሚቹ አካባቢን ከመፍጠር በላይ በጊቢያቸው ዙሪያ እንሰት፣ጎመንና ፍራፍሬ በማዘጋጀት የተትረፈረፈ ማዕድ እንዳላቸው ይገልጻሉ።
ለስራቸው ስኬት ባለቤቶቻቸውና የልጆቻቸው ድጋፍ ከፍተኛ መሆኑንና መንግስት ለዚሁ ስራ እያደረገ ላለው ልዩ ትኩረት ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
ለሌሎች ሰዎችም ተሞክሯቸውንና ልማዳቸውን በማካፈል ውብና ሚቹ አካባቢ እንድፈጥሩ በትኩረት እንደሚሰሩ ሞዴል አርሶ አደሩ አልሸሸጉም።
በሁለገብ ተግባራቸውና በታታሪነታቸው የሚታወቁ አርሶአደር አመነ አምበሎ አዳዲስ ስራን ለአካባቢው ከማሳየት አልፎ የመንግስት ትኩረት አቅጣጫን ቀድሞ በመረዳት ተግባራዊ የሚያደርጉ ሞዴል አርሶ አደር መሆናቸውን ምስክርነት የሰጡት ጎረበትና የቀበሌው አስተዳዳሪ አቶ አየለ አዴሞ ልምዳቸውን ለሌሎች በማጋራት አብሮ ማደግና መለወጥን የሚሹ ጠንካራ ሰው መሆናቸውን ገልጸዋል።
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ
በሸካ ዞን ማሻ ወረዳ በሻይ ምርት አውትግሮውርስ የተደራጁት ወጣቶች ውጤታማ መሆናቸውን ገለጹ።