የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ አገራቸው ጦርነቱን በሰላም ለመቋጨት በተካሄደው የሳውዲ አረቢያ የሰላም ንግግር ላይ እንድትገኝ አለመጋበዟ የሚያስገርም ነው ማለታቸውን ተከትሎ ትራምፕ ጠንከር ያለ ወቀሳ አቅርበዋል።
የዩክሬን ምላሽ ያልጠበቁት እንደሆነ የገለፁት ትራምፕ፤ ለጦርነቱ ጅማሮ ዩክሬንን ተጠያቂ አድርገው አገሪቱ “ስምምነት ላይ መድረስ ትችል ነበር” ብለዋል።
ባለፉት ሶስት ዓመታት ይህን ማድረግ ይችሉ ነበር፤ ችግሩ በቀላሉ ሊፈታ ይችል ነበር ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል።
እንደ ቢቢሲ ዘገባ፥ ዩክሬን ጦርነቱን መጀመር አልነበረባትም፤ ስምምነት ላይ መድረስ ትችል ነበር ብለዋል።
ይህም ከሞላ ጎደል ሁሉንም መሬት ያስገኝላት ነበር፤ ሰዎች አይሞቱም ነበር፣ ከተሞችም አይፈርሱም ነበር ሲሉ ነው ትራምፕ የተናገሩት።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።