የማሻ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ አድሳለም ገብሬ በመድረኩ እንደገለጹት ምክር ቤቶች ህገ-መንግስቱ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ሕግ-አውጭ ፤ሕግ-አስፈፃሚ እና ሕግ-ተርጓሚው ያከናወኗቸውን ተግባራት ለሕዝብ ቀርቦ የሚገመግምበት መሆኑን ተናግረዋል ።
ጉባኤውም የማሻ ወረዳ ምክር ቤት ያለፈውን መደበኛ ጉባኤ ቃሌ ጉባኤ መርምሮ ማፅደቅ፣ የቀረበ ሹመት ማፅደቅን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ከምክር ቤት አባላትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችና ምክክሮች ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
በወረዳው ባለፉት ግማሽ በጀት ዓመትም የተከናውኑ አፈፃፀም ሪፖርት በሚመለከታቸው ባለድሪሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ።
ጉባኤውም ለተከታታይ ሁለት ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል ።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።