የማሻ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ አድሳለም ገብሬ በመድረኩ እንደገለጹት ምክር ቤቶች ህገ-መንግስቱ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ሕግ-አውጭ ፤ሕግ-አስፈፃሚ እና ሕግ-ተርጓሚው ያከናወኗቸውን ተግባራት ለሕዝብ ቀርቦ የሚገመግምበት መሆኑን ተናግረዋል ።
ጉባኤውም የማሻ ወረዳ ምክር ቤት ያለፈውን መደበኛ ጉባኤ ቃሌ ጉባኤ መርምሮ ማፅደቅ፣ የቀረበ ሹመት ማፅደቅን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ከምክር ቤት አባላትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችና ምክክሮች ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
በወረዳው ባለፉት ግማሽ በጀት ዓመትም የተከናውኑ አፈፃፀም ሪፖርት በሚመለከታቸው ባለድሪሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ።
ጉባኤውም ለተከታታይ ሁለት ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል ።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች