የማሻ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ አቶ አድሳለም ገብሬ በመድረኩ እንደገለጹት ምክር ቤቶች ህገ-መንግስቱ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ሕግ-አውጭ ፤ሕግ-አስፈፃሚ እና ሕግ-ተርጓሚው ያከናወኗቸውን ተግባራት ለሕዝብ ቀርቦ የሚገመግምበት መሆኑን ተናግረዋል ።
ጉባኤውም የማሻ ወረዳ ምክር ቤት ያለፈውን መደበኛ ጉባኤ ቃሌ ጉባኤ መርምሮ ማፅደቅ፣ የቀረበ ሹመት ማፅደቅን ጨምሮ በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ ከምክር ቤት አባላትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችና ምክክሮች ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
በወረዳው ባለፉት ግማሽ በጀት ዓመትም የተከናውኑ አፈፃፀም ሪፖርት በሚመለከታቸው ባለድሪሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ይደረጋል ።
ጉባኤውም ለተከታታይ ሁለት ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል ።
More Stories
የ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመስጠት ዝግጅቶች ተጠናቀዋል – የትምህርት ፈተናና ምዘና አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር
የ2017 የፈተና አስተዳደር ስረዓት ዉጤታማ ለማድረግ በየደረጃዉ ያሉ አካላት ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማጠናከር ይገባቸዋል ተባለ።
ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማትና በኮንስትራክሽን በርካታ የሥራ ዕድል እየፈጠረች ነው።