በቢሊየነሩ ኤሎን መስክ የሚመራ ቡድን ኦፕን ኤ.አይ የተባለውን የሰው ሰራሽ አስተውሎት አበልጻጊ ድርጅት በ97 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ለመግዛት ማቀዳቸው ተሰማ።
መስክ ኦፕን ኤ.አይ ትርፋማ ኩባንያ ለመሆን የሚያደርገውን ሽግግር ለመግታት ነው ድርጅቱን ለመግዛት ጥሪ ያቀረበው ተብሏል።
በፈረንጆቹ 2015 ኦፕን ኤአይን ከአሁኑ የድርጅቱ ባለቤት ሳም አልትማን ጋር በጋራ ያቋቋመው መስክ ብዙም ሳይቆይ ድርጅቱን ለቆ መውጣቱ ይታወቃል።
ሰው ሰረሽ አስተውሎት (ኤ.አይ) ደህንነት የተጠበቀ እና ለተጠቃሚዎች ነጻ መሆን እንዳለበት የሚያምነው መስክ በጨረታ በቡድኑ አማካኝነት ድርጅቱን በ97 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ለመግዛት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።
መስክ ያቀረበው ድርጅቱን የመግዛት ጥያቄ ያላስደሰተው የኦፕን ኤ.አይ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሳም አልትማን “ለጥያቄህ እናመሰግናለን አንሸጥልህም ከፈለክ ግን ትዊተርን በ9 ነጥብ 74 ቢሊዮን ዶላር ልንገዛህ እንችላለን” ሲል በኤክስ ባሰፈረው መልእክት ቀልዶበታል።
የኦፕን ኤአይ የቦርድ አባላትም ጥያቄውን ውድቅ ማድረጋቸን ሮይተርስ ዘግቧል።
ሳም አልትማን ኦፕን ኤ.አይን ተርፋማ ድርጅት ለማድረግ፣ አዳዲስ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሞዴሎችን ለመፍጠር እና ኢንቨስተሮችን ለመሳብ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ነው።
ባለፈው ወር ዲፕሲክ የተባለው የቻይና ሰው ሰራሽ አስተውሎት በትንሽ ወጭ፣ በውስን የሰው ኃይል ተገዳዳሪ የሆነ ምርት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ እንደ ኦፕን ኤ.አይ.፣ ጉግልና ሜታ በመሳሰሉ የአሜሪካ ሰው ሰረሽ አስተውሎት አበልጻጊ ኩባንያዎች ሰፈር ድግጋጤ መፍጠሩ ይታወሳል።
More Stories
በህዝቦች መካከል ያለዉን ትስስር ይበልጥ ለማጠናከርና ዘላቂ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የየአካባቢዉን ባህላዊ የግጭት አፈታት ዜዴ በዘላቂነት ማስቀጠል እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ።
የ2018 በጀት ዓመት የካፒታል ፕሮጀክቶች የበጀት ዕቅድ እየተገመገመ ነዉ።
አቶ ጌታቸው ረዳ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ በአዲስ አበባ ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ውይይት እያደረጉ ነው።