ኢትዮጵያ እና ሳውዲ አረቢያ በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ተስማምተዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከሳዑዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ኢ/ር ዋሊድ አብዱልከሪም አልኩራይጂ ጋር በሪያድ ምክክር አድርገዋል። ሁለቱ ወገኖች በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ እና በሁለትዮሽ እና በአለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ትብብር በማድረግ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ተስማምተዋል። በውይይቱ ሁለቱም ወገኖች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር እና ረቂቅ ስምምነቶችን ተግባራዊ ለማድረግ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል
#EBC
More Stories
ከባድ የውንብድና እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል በእስራት ማስቀጣቱን የሸካ ዞን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ85 ሚሊዮን በላይ ብር የህዝብ ሃብት ማዳን ተችላል
ኢትዮጵያ እና ኢንግሊዝ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና ኢኮኖሚ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማሙ