ያለፉት ሁለት ወራት የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲው በስኬታማ አፈፃፀም ላይ መሆኑን ማሳየታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፥ የማክሮኢኮኖሚ ኮሚቴ ዛሬ ጠዋት ተሰብስቦ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም አካል የሆነውንና በቅርብ የተደረገውን የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያዎች አፈፃፀም ገምግመናል ብለዋል።ፖሊሲው ተፈፃሚ በሆነባቸው ሁለት ወራት የተረጋጋ የውጭ ምንዛሪ ከባቢን መመልከት መቻሉንም ገልጸዋል፡፡በተመሳሳይም የገቢ ግባችንም የተቀመጠለትን ግብ በመምታት በታለመለት መንገድ ላይ ይገኛል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)።በአጠቃላይም ያለፉት ሁለት ወራት ፖሊሲው በስኬታማ አፈፃፀም ላይ መሆኑን አሳይተዋል ሲሉም ነው የገለጹት።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።