ሥራአስፈጻሚው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ “ዛሬ ከአዳማ ወደ ጅቡቲ የመጀመሪያ የቁም እንስሳትን በባቡር ወደ ውጭ መላክ እንጀምራለን” ብለዋል፡፡የቁም እንስሳቱን በባቡር ወደ ውጭ ማጓጓዙ በእንስሳት ላይ ያለውን የትራንስፖርት ጫና በመቀነስ የኤክስፖርት ስጋ ጥራትን እንደሚሳድግ አመላክተዋል፡፡ይህም ኢትዮጵያ ለውጤታማ እና ዘላቂ ንግድ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው÷ ኢትዮጵያ በድንበር ላይ የሚደረጉ የካፒታል ፍሰቶችን ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አስረድተዋል(ኤፍ ቢ ሲ)
ከአዳማ-ጂቡቲ የቁም እንስሳት የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ይፋ ሆነከአዳማ ወደ ጂቡቲ የቁም እንስሳት የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ይፋ መሆኑን የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አክሲዮን ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታከለ ኡማ (ኢ/ር) አስታወቁ፡፡

More Stories
” የፕሬስ ነጻነት ቀን ስናከብር ዜጎች በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) መረጃ እንዳይጭበረበሩ ትክክለኛ መረጃ የሚያገኙበት እሳቤ የሚያጎላበት ቀን ሊሆን ይገባል፡፡”
አራተኛው ዙር የኢራን እና የአሜሪካ ድርድር ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ
የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የስራ ኃላፊዎች የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ የስራ አፈጻጸምን ተመለከቱ