የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና የሚኒስቴሩ የሥራ ኃላፊዎች ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራምን ጎብኝተዋል። ሚኒስትሯ እና ኃላፊዎቹ ከፕሮግራሙ አመራሮች ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከጤና ዘርፍ ጋር ስለሚኖረው ትሥሥር ተወያይተዋል። በቀጣይ ብሔራዊ መታወቂያ ለጤናው ዘርፍ በሚጠቅምበት ጉዳይ ላይ አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነትም ተፈራርመዋል።የሥራ ጉብኝት ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ እና የሥራ ኃላፊዎቹ ለፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ማድረጋቸውንም ከብሔራዊ መታወቂ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
የጤና ሚኒስቴር እና ብሔራዊ መታወቂያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ