የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ 837 መኖሪያ ቤቶችን ለአቅመ ደካሞች እና ለሀገር ባለውለታ ነዋሪዎች አስተላልፈዋል።
ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብተው ለነዋሪዎች ከተላለፉ ቤቶች ውስጥ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በየካ ክፍለ ከተማ 54 ቤቶችን የገነባ ሲሆን ለዚህም ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልን አመሰግናለሁ ብለዋል።
እንዲሁም በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ በተለያዩ ባለሀብቶች 108 ቤቶች፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ በአብዱለጢፍ ዑመር ፋውንዴሽን (አሚባራ ግሩፕ) 32 ቤቶች መገንታቸውን እና ሁሉም ቤቶች ለነዋሪዎች መተላለፋቸውን ገልፀዋል።
ነዋሪዎች አዲስ ዓመትን በአዲስ ተስፋ እንዲጀምሩ ትልቅ አስተዋፅዖ ያበረከታችሁ ተቋማት እና የከተማችን ልበ ቀና ባለሃብቶችን በራሴ፣ በከተማ አስተዳደሩ እና በነዋሪዎቹ ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ ብለዋል ከንቲባዋ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ 837 መኖሪያ ቤቶችን ለአቅመ ደካሞች እና ለሀገር ባለውለታ ነዋሪዎች አስተላለፉ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።