በሥነጥበብ፣ በታሪክ እና በቅርስ ጠባቂነት፣ በንግግር አዋቂነት፣ በድርሰት ሥራዎቻቸው፣ በላቀ የምህድስን በሙያቸው እንዲሁም በበጎ አድራጊነት ሥራቸው ይታወቃሉ፡፡ ታታሪነትና እና ሀገርን መውደድ በተግባር ያሳዩን ሁለገብ ባለሙያ፣ ሁሉም በየዘርፉ እና በየአቅሙ ለሀገሩ ምን ማበርከት እንዳለበት ሠርተው ያሳዩ ሊቅ ናቸው፡፡ መኖሪያ ቤታቸው የኢትዮጵያ ባለውለታ የሆኑ ታላላቅ ሰዎችን በሚዘክሩ ታሪካዊ እና ዕድሜ ጠገብ ሥዕላት፣ ምስሎች እና ፎቶግራፎች፣ ቅርጻ ቅርጾች እንዲሁም የኢትዮጵያን ታሪክ እና ቅርስ በተመለከተ በጽሑፎች፣ በሰነድ፣ በምስል፣ በድምፅ እና በቪዲዮ ያሰባሰቧቸው መረጃዎችና ቅርሶች የተሞላ እንደሆነ የቅርብ ወዳጆቻቸው ይመሰክራሉ። ለኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ቅርስ ያላቸው ክብር እና ተቆርቋሪነት እንዲሁም ለሕዝባቸው ያላቸው ፍቅር እናወገናዊነት በጣም ጥልቅ ነው ይባልላቸዋል።
EBC
More Stories
በጤና ተቋማት የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችን በመከላከልና ተገቢውን የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ትኩረት ማድረግ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ይጠበቃል ተባለ ።
ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት ሁለተኛውን የዓርበኝነት ምዕራፍ ጀምራለች – ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ኢትዮጵያ እያስመዘገበችው ላለው ፈጣን እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው፦ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር)