የቴፒ ከተማ ምክር ቤት አያካሄደ ባለዉ 2ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤዉ የከተማውን የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምንና የ2017 ዕቅድና የማስፈፀሚያ በጀት ቀርቦ ተወያይቶ አፅድቋል።
የቴፒ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ተካልኝ ሻወኖ የፍርድ ቤቱን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምንና የ2017 ዕቅድና የማስፈፀሚያ በጀት ለጉባኤዉ አቅርበዉ በአባላቱ ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶበታል።
በዚህም በ2016 በጀት ዓመት በጥቅል 1 ሺህ 1 መቶ 97 መዝገቦች ቀርበው በፍትሀብሔርና በወንጀል 1 ሺህ 1 መቶ 84ቱ ላይ ውሳኔ መስጠት መቻሉን ተናግረዉ ቀሪዉ 13 መዝገቦች በቀጣይ እንዲታዪ መዘዋወራቸዉን አንስተዋል።
በተያያዘም በ 2017 ዕቅድ ማስፈፀሚያ በጀት ከ 9 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ሆኖ ቀርቦ በምክር ቤቱ ሙሉ ድምፅ ቀርቦ ፀድቋል።
ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።