የቴፒ ከተማ ምክር ቤት አያካሄደ ባለዉ 2ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤዉ የከተማውን የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምንና የ2017 ዕቅድና የማስፈፀሚያ በጀት ቀርቦ ተወያይቶ አፅድቋል።
የቴፒ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ተካልኝ ሻወኖ የፍርድ ቤቱን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምንና የ2017 ዕቅድና የማስፈፀሚያ በጀት ለጉባኤዉ አቅርበዉ በአባላቱ ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶበታል።
በዚህም በ2016 በጀት ዓመት በጥቅል 1 ሺህ 1 መቶ 97 መዝገቦች ቀርበው በፍትሀብሔርና በወንጀል 1 ሺህ 1 መቶ 84ቱ ላይ ውሳኔ መስጠት መቻሉን ተናግረዉ ቀሪዉ 13 መዝገቦች በቀጣይ እንዲታዪ መዘዋወራቸዉን አንስተዋል።
በተያያዘም በ 2017 ዕቅድ ማስፈፀሚያ በጀት ከ 9 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ሆኖ ቀርቦ በምክር ቤቱ ሙሉ ድምፅ ቀርቦ ፀድቋል።
ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።