የቴፒ ከተማ ምክር ቤት አያካሄደ ባለዉ 2ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤዉ የከተማውን የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምንና የ2017 ዕቅድና የማስፈፀሚያ በጀት ቀርቦ ተወያይቶ አፅድቋል።
የቴፒ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ተካልኝ ሻወኖ የፍርድ ቤቱን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀምንና የ2017 ዕቅድና የማስፈፀሚያ በጀት ለጉባኤዉ አቅርበዉ በአባላቱ ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶበታል።
በዚህም በ2016 በጀት ዓመት በጥቅል 1 ሺህ 1 መቶ 97 መዝገቦች ቀርበው በፍትሀብሔርና በወንጀል 1 ሺህ 1 መቶ 84ቱ ላይ ውሳኔ መስጠት መቻሉን ተናግረዉ ቀሪዉ 13 መዝገቦች በቀጣይ እንዲታዪ መዘዋወራቸዉን አንስተዋል።
በተያያዘም በ 2017 ዕቅድ ማስፈፀሚያ በጀት ከ 9 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ሆኖ ቀርቦ በምክር ቤቱ ሙሉ ድምፅ ቀርቦ ፀድቋል።
ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።