የኢትዮጵያ አየር መንገድ የባንግላዲሽ ዋና ከተማ ወደሆነችው ዳካ አዲስ በረራ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡አየር መንገዱ ወደ ዳካ ከተማ ከጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሳምንት ስድስት ቀናት አዲስ በረራ እንደሚጀምር በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡የበረራ መስመሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በደቡብ እስያ ያለውን ተደራሽነት የሚያሰፋ ሲሆን በባንግላዴሽ እና አፍሪካ መካከል ብሎም ከተቀረው ዓለም ጋር የሚደረገውን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑ ተመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ባለፉት ሦስት ዓመታት ለሰብዓዊ ድጋፍ በሚል የገባ ስንዴ የለም – አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር)
በገጠሩ የሀገሪቱ አካባቢዎች መንግስት የሚዘረጋቸውን የተለያዩ ኢንሸቲቦችን ቀድሞና ፈጥኖ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር የተሻሉ አፈጻጸሞች መታየታቸው ተገለፀ ።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ6 ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳለፈ