ቦይንግ 757-232 የሚል የምርት መለያ ያለው አውሮፕላኑ የአሜሪካው ዴልታ አየር መንገድ ንብረት ሲሆን በአትላንታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለሶስት ቀናት የቴክኒክ ጥገና ሲደረገለት እንደነበር ተመላክቷል፡፡አውሮፕላኑ በጥገና ላይ በነበረበት ወቅት ጎማው በመፈንዳቱ ሁለት የጥገና ሰራተኞች ሲሞቱ በተጨማሪ ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ማስከተሉም ተገልጿል።የአውሮፕላኑ የጎማ ፍንዳታ መንስዔ አለመታወቁን የገለጸው የአር ቲ ዘገባ፤ የቦይንግ አውሮፕላን በየጊዜው የሚያጋጥሙት የቴክኒክ ችግሮች በርካታ አደጋዎችን ከማስከተሉ ባለፈ ለደንበኞች ደህንነት ስጋት እየሆኑ እንደሆነ ጠቅሷል።
በአሜሪካ አትላንታ የቦይንግ አውሮፕላን ጎማ ፈንድቶ ሁለት የጥገና ሰራተኞች ህይወት ማለፉ ተገለፀ፡፡
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።