ቦይንግ 757-232 የሚል የምርት መለያ ያለው አውሮፕላኑ የአሜሪካው ዴልታ አየር መንገድ ንብረት ሲሆን በአትላንታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለሶስት ቀናት የቴክኒክ ጥገና ሲደረገለት እንደነበር ተመላክቷል፡፡አውሮፕላኑ በጥገና ላይ በነበረበት ወቅት ጎማው በመፈንዳቱ ሁለት የጥገና ሰራተኞች ሲሞቱ በተጨማሪ ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ማስከተሉም ተገልጿል።የአውሮፕላኑ የጎማ ፍንዳታ መንስዔ አለመታወቁን የገለጸው የአር ቲ ዘገባ፤ የቦይንግ አውሮፕላን በየጊዜው የሚያጋጥሙት የቴክኒክ ችግሮች በርካታ አደጋዎችን ከማስከተሉ ባለፈ ለደንበኞች ደህንነት ስጋት እየሆኑ እንደሆነ ጠቅሷል።
በአሜሪካ አትላንታ የቦይንግ አውሮፕላን ጎማ ፈንድቶ ሁለት የጥገና ሰራተኞች ህይወት ማለፉ ተገለፀ፡፡
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።