የአሽንዳ በዓል ባህላዊ እና ኃይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ መሆኑን፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል፡፡ ቢሮው በዓሉን አስመልክቶ የሴቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማሳደግ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት አካሄዷል፡፡ በፓናል ውይይቱ ላይ አሸንዳን የቱሪስት መስህብ ማድረግ በሚቻልበት አግባብ ላይ ምክክር ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይ የአሸንዳ የካርኒቫል ሥነ-ሥርዓት መካሄዱ ታውቋል፡፡ በነገው ዕለትም የጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ እንግዶች በተገኙበት የአሸንዳ በዓል በድምቀት እንደሚከበር ተመላክቷል፡፡
የአሽንዳ በዓል እሴቱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ ነው – የትግራይ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …