የአሽንዳ በዓል ባህላዊ እና ኃይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ መሆኑን፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል፡፡ ቢሮው በዓሉን አስመልክቶ የሴቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማሳደግ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት አካሄዷል፡፡ በፓናል ውይይቱ ላይ አሸንዳን የቱሪስት መስህብ ማድረግ በሚቻልበት አግባብ ላይ ምክክር ተደርጓል፡፡ በተመሳሳይ በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይ የአሸንዳ የካርኒቫል ሥነ-ሥርዓት መካሄዱ ታውቋል፡፡ በነገው ዕለትም የጊዜያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች እና ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ እንግዶች በተገኙበት የአሸንዳ በዓል በድምቀት እንደሚከበር ተመላክቷል፡፡
የአሽንዳ በዓል እሴቱን ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ እየተሰራ ነው – የትግራይ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች