የአሰላ የንፋስ ኃይል በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ በኢተያ ከተማ አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከሚተከሉ 29 ተርባይኖች የ13ቱ ተከላ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ክትትልና ቁጥጥር ባለሙያ ገለፁ፡፡ ባለሙያው አቶ ይድነቃቸው ደሳለኝ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 61 በመቶ ደርሷል። በፕሮጀክቱ ከሚተከሉት 29 የንፋስ ማማዎች ውስጥ የ23ቱ የመሰረት ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን አፈፃፀሙም 80 በመቶ መድረሱን ጠቁመዋል። 16 የንፋስ ማማዎችን ለመትከል የሚያስችሉ ዕቃዎች ከወደብ ተጓጉዘው ሳይት መድረሳቸውንም ነው አቶ ይድነቃቸው የገለፁት።
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።