የአሰላ የንፋስ ኃይል በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ በኢተያ ከተማ አካባቢ እየተገነባ የሚገኘው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከሚተከሉ 29 ተርባይኖች የ13ቱ ተከላ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ክትትልና ቁጥጥር ባለሙያ ገለፁ፡፡ ባለሙያው አቶ ይድነቃቸው ደሳለኝ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀም 61 በመቶ ደርሷል። በፕሮጀክቱ ከሚተከሉት 29 የንፋስ ማማዎች ውስጥ የ23ቱ የመሰረት ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን አፈፃፀሙም 80 በመቶ መድረሱን ጠቁመዋል። 16 የንፋስ ማማዎችን ለመትከል የሚያስችሉ ዕቃዎች ከወደብ ተጓጉዘው ሳይት መድረሳቸውንም ነው አቶ ይድነቃቸው የገለፁት።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች