የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ ተፈጥሮ በነበረው የመሬት መንሸራተት በደረሰው አደጋ የተጎዱ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም የተጀመሩ ስራዎችን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡ ችግሩ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የክልሉ መንግስት ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ ኮሚቴዎችን በማቋቋም የአስቸኳይ ጊዜ ስራዎች ብሎም በዘላቂነት የሚፈጸሙ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ተገልጿል። በዚህም በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን÷ የተሰበሰበውን ሀብት በአግባቡ በመያዝ ደረጃውን የጠበቀ ስርጭት እና የአስተዳደር ስርአት መከተል እንደሚገባ አቶ ጥላሁን ተናግረዋል። በአደጋው የተጎዱ ሰዎች ቤተሰቦችን በዘላቂነት ለማስፈር እና መልሶ ለማቋቋም እየተከናወነ የሚገኘው የመኖሪያና የእርሻ ቦታ መረጣና ዝግጅት በጥናት የተደገፈ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሂደቱም የህዝቡን ተሳትፎ ያረጋገጠ እንዲሆን ርዕሰ መስተዳድሩ ማሳሰባቸውን ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች