የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ ተፈጥሮ በነበረው የመሬት መንሸራተት በደረሰው አደጋ የተጎዱ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም የተጀመሩ ስራዎችን በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡ ችግሩ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ የክልሉ መንግስት ከተለያዩ ተቋማት የተውጣጡ ኮሚቴዎችን በማቋቋም የአስቸኳይ ጊዜ ስራዎች ብሎም በዘላቂነት የሚፈጸሙ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ተገልጿል። በዚህም በአደጋው ለተጎዱ ወገኖች የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን÷ የተሰበሰበውን ሀብት በአግባቡ በመያዝ ደረጃውን የጠበቀ ስርጭት እና የአስተዳደር ስርአት መከተል እንደሚገባ አቶ ጥላሁን ተናግረዋል። በአደጋው የተጎዱ ሰዎች ቤተሰቦችን በዘላቂነት ለማስፈር እና መልሶ ለማቋቋም እየተከናወነ የሚገኘው የመኖሪያና የእርሻ ቦታ መረጣና ዝግጅት በጥናት የተደገፈ መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል። ሂደቱም የህዝቡን ተሳትፎ ያረጋገጠ እንዲሆን ርዕሰ መስተዳድሩ ማሳሰባቸውን ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።